ጉዳዩ፡- የብሄራዊ ድህረ-ምረቃ (NGAT) መግቢያ ፈተና ቀንን
ስለማሳወቅ
በ2017 ዓ.ም የሶስተኛ ዙር የNGAT አመልካቾች ምዘገባ ተጠናቅቋል፡፡ በዚሁ መሰረት ለመፈተን ያመለከታችሁ አመልካቾች ፈተናው የሚሰጠው ዓርብ መጋቢት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በምትመደቡበት የፈተና ማዕከላት እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-
- ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከል በምትሄዱበት ወቅት ማንነታችሁን የሚገልጽ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
- ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከመጀመሩ 3 ደቂቃ በፊት በፈተና ማዕከል መገኘት ይጠበቅበታል፡፡
- የሞባይል ስልክ ይዞ በፈተና ማዕከል መገኘት ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
- የፈተና ማዕከላት ምደባ በምዝገባ ፕላትፎርም የሚገለጽ ይሆናል፡፡